ጥር 12 ቀን 2007 ዓ.ም.
ዲ/ን ዘአማኑኤል አንተነህ /ከጎንደር ማእከል/
የ2007 ዓ.ም. አከባበሩም የሚከተለውን ይመስል ነበር፡-
ነሐሴ 5 ቀን 2007 ዓ.ም ምንጭ፡ ማኅበረ ቅዱሳን http://eotcmk.org/site/-mainmenu-24/--mainmenu-26/1953-2015-08-11-05-46-55 |
በዘአማኑኤል አንተነህ/ከጎንደር ማእክል/
፩.ታሪክ
ዐፄ ዮስጦስ የአድያም ሰገድ ኢያሱ የእህት ልጅ ፣ የፃድቁ ዮሐንስ የልጅ ልጅ ናቸው፡፡ አባታቸው ደጃዝማች ድል በኢየሱስ ይባላሉ፣ እናታቸው በውል አይታወቁም፡፡ ዐፄ ዮስጦስ የጎንደር ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያንን የተከሉ እና በጥምቀት ጊዜ እመቤታችን የተገለፀችላቸው ንጉሥ ናቸው፡፡ ዐፄ ዮስጦስ በንግሥናቸው ወቅት ከሱዳኖች ጋር በነበራው ግንኙነት ሱዳኖች አንገብርም እያሉ ያስቸግሯቸው ነበር፡፡ ቱርኮች እና ግብጾች እየመጡም ሱዳኖችን አትገብሩ እያሉ ይሰብኳቸው ነበር፡፡ በአብርሃ ወአጽብሐ ዘመነ መንግሥት ሱዳኖች አንገብርም እያሉ በነበረበት ወቅት አብርሐ ወአጽብሐ ሒደው 5000 ግመል አመጡ እየተባለ ይነገርላቸዋል፡፡ በዐፄ ዮስጦስ ንግሥና ዘመንም ሱዳኖች አንገብርም በማለታቸው ንጉሡ ቸር አድርሰሽ ድል አድርጌ የመለስሽኝ እንደሆነ በየዓመቱ እዘክራለሁ ብለው ተስለው (ብጽዓት ገብተው) ወደ ጦርነቱ ሄዱ፡፡ ድል አድርገው ከተመለሱ በኋላ ሱባኤ ፍልሰታን ማታ ማታ መኳንንቱን ሰብስበው መዘከር ጀመሩ፡፡ ስያሜውንም አድርሽኝ በማለት ሰየሙት፡፡ |
|
ከጎንደር ማእከል
በማኅበረ ቅዱሳን ጎንደር ማእከል በቅዱሳት መካናት እና ማኅበራዊ አገልግሎት ክፍል አዘጋጅነት â¹â¹ዘላቂ ልማት ለገዳማት እና ለአብነት ት/ቤቶቻችንâºâº በሚል መሪ ቃል በጎንደር ከተማ ሲኒማ አዳራሽ ሐምሌ 4 ቀን 2007 ዓ.ም የውይይት መርሐ ግብር ተካሄደ፡፡
ጉባኤው ቅዳሜ ከሰዓት 8፡00 ላይ የተጀመረ ሲሆን፤ ጉባኤውን የከፈቱት ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ናቸው፡፡ ብፁዕነታቸው በመክፈቻ ንግግራቸው የአብነት ት/ቤቶቻችን የማንነታችን መገለጫና የሀገሪቱ የሊቃውንት መፍለቂያ ማኅፀን እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡ |
መስከረም 7 ቀን 2008 ዓ.ም
ምንጭ፡ ማኅበረ ቅዱሳን http://eotcmk.org/site/-mainmenu-18/1995-2015-09-18-18-35-44
ዲ/ን ዘአማኑኤል አንተነህ /ከጎንደር ማእከል/
መንፈሳዊ በዓላትን መንፈሳዊ ይዘታቸውን ጠብቆ ከማክበር ባለፈ የተቸገሩ ወገኖችን ማስታወስና መጎብኘት ሃይማኖታዊ ግዴታ እንደሆነ ቤተ ክርስቲያናችን ለዘመናት ስትሰብክ ኖራለች ወደፊትም ትቀጥላለች፡፡ ሕዝበ ክርስቲያኑም ይህንን መሠረት በማድረግ በየበዓላቱ ነዳያንን በመጎብኘት፤ አብሮ በዓላትን በማክበር ችግሮቻቸውን በመጋራት ድጋፍ ያድርጋል፡፡ |
መስከረም 14ቀን 2008 ዓ.ም
ምንጭ፡ ማኅበረ ቅዱሳን http://eotcmk.org/site/-mainmenu-24/---mainmenu-27/2002-2015-09-25-06-33-41
ዘአማኑኤል አንተነህ
አባቶቻችን Â መንፈሳዊና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረተ ሐሳቦች ላይ በመመሥረት ነጠላን እንለብስ ዘንድ ሥርዐትን ሠሩልን::
1.ጌታን አብነት በማድረግ
ጌታ ከደቀ መዛሙርቱ መካከል የምሥጢር ሐዋርያት የሚባሉትን ጴጥሮስን ፣ ዮሐንስንና ያዕቆብን ይዞ ወደ ደብረ ታቦር ወጥቶ ደቀ መዛሙርቱ እያዩት ልብሱ ነጭ ሆኖ ነበር፤"በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ።"(ማቴ17:2) እኛም ሊያድነንና አርአያ ሆኖ ሊያስተምረን ሰው የሆነውን ጌታችንን አብነት በማድረግ ነጭ ነጠላን ለብሰን የደብረ ታቦር ምሳሌ ወደሆነችው ቤተክርስቲያን እንሰባሰባለን። |